
ፍቅር እስከ ጀነት (𝐑𝐚𝐦𝐚𝐬)
ደረሳው !
የደረሳ ሕይወት በእውቀት ብርሃንና በናፍቆት እንባ የተገመደ ለምድራዊ ምቾት ባዕድ የሆነ የነፍስ ተጋድሎ ነው። እነዚህ የጥበብ መንገደኞች ሆዳቸው በራብ እየተቆረጠ አካላቸው በብርድ እየተገረፈና ለምድራዊ ሂወት ጀርባ ሰጥተው ሌሊቱን በሙሉ በትንሿ ኩራዝ (ፋኖስ) ብርሃን ኪታባቸውን ሲያገላብጡ ያድራሉ። በየደጁ የሚለምኗት "ቀለብ" ክብራቸውን የምታሳንስ ሳይሆን ለኢልም ያላቸውን ዝቅታና ትህትና የምታሳይ የትዕግሥታቸው ማህተም ናት። እያንዳንዷን የኪታብ ገጽ ሲገልጡ በቃላቸው የሚሸመድዱት እውቀት የነገው የኡማው ብርሃን መሆኑን ያውቃሉ ። ለዚህም ነው እናትና አባታቸውን የትውልድ መንደራቸውንና የልጅነት ጓደኞቻቸውን ትተው በየመስጂዱ ጥግና በየዛፉ ስር በባዶ መሬት ላይ እየተንከባለሉ የጥበብን ማር የሚቀስሙት።
ከሁሉ በላይ ግን የደረሳን ልብ የሚያቀልጠውና በመከራ ውስጥ ሆነው ፈገግታን የሚለግሳቸው ለነቢዩ ሙሐመድ ሰላሏህ ወአለይሂ ወሰለም ያላቸው ወደር የለሽ ፍቅር ነው። በግጥማቸው ውስጥ "ያ ረሱለላህ!" ብለው ሲጣሩ ያ ከጥልቅ የልብ ስብራት የሚወጣው ድምፅ ሰማይንና ምድርን የሚያናውጥ የናፍቆት እሳት ነው። ለረሱል ሰላሏህ ወአለይሂ ወሰለም ያላቸው ሙሀባ ከቃላት በላይ ነው። በሰለዋት የታጀበው ለቅሶአቸውና በሳቸው ስም የሚፈሰው እንባቸው የደረሳው አካል በረሀብ ቢዝልም ነፍሱ ግን በሳቸው ፍቅር እንደምታብብ ምስክር ነው። ለእነሱ ረሱል ሰላሏህ ወአለይሂ ወሰለም የመንገዳቸው መሪ ብቻ ሳይሆኑ በብቸኝነትና በስደት ህይወታቸው ውስጥ የሚታዩአቸው ብቸኛ የብርሃን ጥላ ናቸው። ይህ በኢልምና በሙሀባ መካከል የተሰነቀው የደረሳ ሕይወት ዛሬም ድረስ በገጠር መስጂዶች ውስጥ የሚሰማ ሕያውና ልብ የሚነካ የፍቅር ታሪክ ነው።
╭┈─────── ೄ
🌹
ྀ࿐ ˊˎ-
~
t.me/FKR_ESKE_JENET
🎊
የድል ብስራት !
🎊
"ረሱል (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)" በሚል ርዕስ ተዘጋጅቶ በነበረው ታላቅ የግጥም ውድድር ላይ ብርቱ ፉክክር ሲደረግ ቆይቶ አሸናፊው በይፋ ታውቋል!
በጥበብ የታጀበ ለነቢዩ (ሰለሏህ ወአለይሂ ወሰለም ) ያለውን ጥልቅ ፍቅር በግጥም ስንኞች ያፈሰሰውና የዳኞችን ቀልብ የሳበው፦
🏆
ሁሴን ጀማል
ከደሴ
🏆
የውድድሩ
የአንደኛ ደረጃ አሸናፊ
በመሆን ለዚህ የላቀ ክብር በቅቷል።
ሁሴን ጀማ
ል እንኳን ደስ አለህ! ብዕርህ ይባረክ ጥበብህም ለሌሎች ብርሃን መሆኑን ይቀጥል። በነቢዩ ታሪክ ላይ እንዲህ ችሎታህን ማሳየትህ ትልቅ ስኬት ነው።
በውድድሩ ላይ ለተሳተፋችሁ እና ድምፅ በመስጠትም ሆነ በማበረታታት አብራችሁን ለነበራችሁ ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነው።
እኔ አልችልበትም...
ለጊዜያዊ ጥቅም ብዬ ቃላቶቼን በውሸት ማር ለውሼ ሰውን ማባበል፣ በሐሰት አሳምኖ ሰውን ከጎን ማቆየት፣ እውነትን ደብቆ ውሸትን ማንገስ፣የሌለ ማንነትን እንደ ጌጥ ተከናንቦ መታየት፣ አዎ እኔ አልችልበትም!
ሰውን አታልዬ በዙሪያዬ ከማሰባሰብ፣ በእውነተኛነቴና በቅንነቴ አጥቼ ከራሴ ጋር በሰላም ብቻዬን ብቀር እመርጣለሁ፡፡
╭┈─────── ೄ
🌹
ྀ࿐ ˊˎ-
~
t.me/FKR_ESKE_JENET
ትክክለኛ እውነቱ የሚገባን ሰው የነገረን ነገር ሳይሆን ጊዜ ራሱ መልሱን ሲሰጠን ነው !
@FKR_ESKE_JENET
የግጥም ውድድሩ ነገ 3 ሰአት የሚጠናቀቅ ይሆናል ጠንካራ ተፎካካሪዎች አሉ ። መልካም እድል ለሁላችሁም !