
Sheger Press️️
የቻይና "ሚስጥራዊ" የጦር መሣሪያዎች አሜሪካን ስጋት ላይ ጥለዋል
ተባለ
‼
- ፕሬዝደንት ትራምፕ ትናንት ምሽት ቻይና ገብተዋል
‼
ቻይና በቴክኖሎጂ የረቀቁና የዓለምን ወታደራዊ ሚዛን ሊቀይሩ የሚችሉ አዳዲስ የጦር መሣሪያዎችን ይፋ ማድረጓ የአሜሪካን ስጋት ጨምሮታል።
ከእነዚህም መካከል፦
- ከድምፅ ፍጥነት በ5 እጥፍ የሚፈጥነውና ማንኛውንም መከላከያ ሰብሮ የሚገባው DF-17 ሚሳይል፣
- የአሜሪካን የባህር ላይ የበላይነት የሚገታው "የአውሮፕላን ተሸካሚ መርከቦች ገዳይ" ሚሳይል፣
- እንዲሁም የጠላትን ሳተላይቶችና ጂፒኤስ (GPS) የሚያሳውሩ ቴክኖሎጂዎች ዋነኞቹ ናቸው።
በተጨማሪም በመቶዎች የሚቆጠሩ ድሮኖችን እንደ ንብ መንጋ በማሰማራት መከላከያን ሽባ የሚያደርገው Drone Swarm ቴክኖሎጂ ቻይና በዘመናዊ ጦር መሣሪያ ልማት የደረሰችበትን ከፍተኛ ደረጃ የሚያሳይ መሆኑ ተገልጿል።
በአፍሪካ ቀንድ እየተባባሰ የመጣውን ውስብስብ ጂኦ-ፖለቲካዊ ቀውስ ተከትሎ፣ የኢትዮጵያ መንግስት እና የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ባለስልጣናት በዋሽንግተን ዲሲ ወሳኝ ውይይት አካሂደዋል።
ይህ ወቅታዊ እና ትኩረት የሚሻ ስብሰባ የተካሄደው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) እና የአሜሪካ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ጉዳይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ከሆኑት ኮንግረስማን ብራያን ማስት ጋር ነው። የውይይቱ ዋና ማጠንጠኛ ቀጠናው በአሁኑ ወቅት የተጋረጡበትን የጸጥታ እና የፖለቲካ ፈተናዎች በጋራ መፍታት በሚቻልበት መንገድ ላይ ያተኮረ ነበር።
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ሁለቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በአፍሪካ ቀንድ ስላለው የቅርብ ጊዜ አጠቃላይ የፖለቲካ እና የጸጥታ ሁኔታ በዝርዝር መክረዋል። ቀጠናው ከውስጣዊ የፖለቲካ አለመረጋጋት፣ ከድንበር ተሻጋሪ ሽኩቻዎች እንዲሁም ከተደራራቢ የዲፕሎማሲ ፈተናዎች ጋር እየታገለ ባለበት በዚህ ወሳኝ ወቅት፣ የሁለቱ ሀገራት የፊት ለፊት ግንኙነት ከፍተኛ ሀገራዊ እና ቀጠናዊ ፋይዳ አለው።
ይህ ውይይት የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅም ከማስጠበቅ ባሻገር፣ አሜሪካ በቀጠናው ያላትን የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ፍላጎት ለማመጣጠን የሚደረግ ጥረት አካል መሆኑን ያሳያል።
በዚህ የጋራ ምክክር ላይ ሁለቱም ወገኖች አንድ ትልቅ ስምምነት ላይ መድረሳቸው ተገልጿል። ይኸውም በቀጠናው ለሚታዩት ውስብስብ እና አሳሳቢ ፈተናዎች ጊዜያዊ ማስታገሻ ሳይሆን፣ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ መፍትሄ ለማምጣት የጠበቀ የጋራ ቅንጅት እና ትብብር ማድረግ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ማመናቸው ነው። ከዚህ ቀደም የነበሩ አለመግባባቶችን ወደ ጎን በመተው ወደ የጠበቀ ትብብር መምጣታቸው፣ በኢትዮጵያ እና በአጠቃላይ በአፍሪካ ቀንድ የሰላም ግንባታ እና መረጋጋት ላይ በተጨባጭ መሬት ላይ የሚወርድ አዎንታዊ ለውጥ ያመጣል ብላችሁ ታስባላችሁ? አስተያየት ስጡት።
እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም
🙏
ወላጆቻቸው ልጅ አጥተው ሠላሳ ዘመን ሲያዝኑ ኖረዋል፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ይባላሉ፡፡ አንድ ቀን አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥዕለ ሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን ታላቅ ክብር ያለው ልጅ እንደምትወልድ የሚናገር ድምጽ ሰማች፡፡ በመጋቢት 29 ቀን ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ቀን ደም ግባቱ እጅግ የሚያምር ወንድ ልጅ ግብጽ ንሂሳ በምትባል ቦታ ወለደች፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡ ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገደ፡፡ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ ከዚህ በኋላ እናታቸው አላቀፈቻችውም፤ ጡትም አልጠቡም፡፡
ሦስት ዓመት ሲሞላቸውም ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ ሕፃኑን ከእናቱ ክንድ ወስዶ እስከ ሰባቱ ሰማይ አውጥቶ በሥሉስ ቅዱስ ፊት አቅርቦት አስባረከው፡፡ እመቤታችን፣ ቅዱሳንም ሁሉ ባረኩት፡፡ አምላካችን እግዚአብሔርም አጸናው አበረታው፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ አባ ዘመደ ብርሃን ወዳለበት ገዳም አወረደው እርሱም አስተምሮ ካሳደገው በኋላ ዲቁና በኋላም ምንኩስናና ቅስና ሰጠው፡፡ ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡ የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸው፡፡ ከሰው ተለይተው ከአናብስትና ከአናብርት ጋር እንዲኖሩ፣ እንስሳቱም የእግራቸውን ትቢያ እየላሱ እንደሚኖሩ ነገራቸው፡፡
ሰውነታቸውም ሁሉ በጠጉር ተሸፈነ፡፡ በፍጹም ተጋድሎም ከኖሩ በኋላ በቀንና በሌሊት የክርስቶስን መከራ እያሰቡ ስለኃጥአንም ጥፋት እንባቸውን እያፈሰሱ ይጸልዩ ነበር፡፡ ሦስት መቶ ዓመት ሲሆናቸውም ቅዱስ ገብርኤል በነፋስ ሠረገላ ጭኖ ከ60 አንበሶችና ከ60 ነብሮች ጋር ወደ ኢትዮጵያ አምጥቶ ምድረ ከብድ አደረሳቸው፡፡ ደብር ቅዱስ ወደሚባለው ዝቋላም ሔደው የኢትዮጵያን ሕዝብ ማርልኝ ብለው ለአንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው ስጋቸው እስኪያልቅ ጸልየዋል፡፡ ጌታችንም መጥቶ ኢትዮጵያን ምሬልሀለሁ ብሎ ታላቅ ቃል ኪዳን ሰጣቸው፡፡ አባታችን በሀገራችን 262 ዓመታት ኖረው በተወለዱ በ562 ዓመታቸው በዕለተ እሁድ አርፈዋል፡፡ በቅዱሳኑ ምልጃ ያመንን ገዳማውያንን እንደግፍ በዓታቸውን እናጽና፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
ለበለጠ መረጃ:- 09 38 64 44 44/0918077957
"በሳዑዲ በሞት ጥላ ሥር ላሉ ኢትዮጵያውያን ምሕረት እንዲደረግ እንጠይቃለን" አቡነ ማትያስ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያሊክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በሳዑዲ ዓረቢያ የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው ወገኖችን በማስመልከት ጥሪ አስተላለፉ።
የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳዑዲ ባለሥልጣናት ጋር በከፍተኛ ደረጃ ተነጋግሮ የሞት ፍርዱ እንዲነሳና ወገኖቻችን ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥም አሳስበዋል።
በፖሊስ አባል ህይወቱ ለጠፋው ግለሰብ ቤተሰቦች የመኖሪያ ቤትና የመሥሪያ ቦታ ተሰጠ
በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 በፖሊስ አባል ህይወቱ ያለፈው የአቶ ተገኝ ባልቻ ቤተሰቦች፣ ከአዲስ አበባ አስተዳደር የመኖሪያ ቤትና የመሥሪያ ቦታ ርክክብ ተደረገ።
መረጃ
‼️
ዶ/ር ገብሩ ካህሳይ ወደ አልታወቀ ቦታ ተወሰዱ
‼️
ከሰሞኑ ዶክተር ደብረፅዮንን የክልሉ ፕሬዚደንት አድርጎ የሾመዉ የህወሓት ቡድን፣ የጄኔራል ታደሰ ወረደ ደጋፊዎች ናቸዉ ተብለዉ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ማሰር መጀመሩ ተሰምቷል፡፡
በዚህም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ቢሮ የፕሬስ ሴክሬታሪያት ኃላፊ ዶ/ር ገብሩ ካህሳይ ግንቦት 03/2018 ዓ.ም ከምሽቱ 3፡00 በመቀሌ ከተማ 'ዲያስፖራ' በተባለ አከባቢ ላይ በቡድኑ ታጣቂ አባላቶች ታፍነዉ መወሰዳቸዉ ታዉቋል።
(Ayu)
"ኢራን የጉልበተኞች ተቃዋሚ እንጂ ጉልበተኛ አይደለችም" የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባጋኢ፣ ሀገራቸው በቀጠናው ኃላፊነት የሚሰማት ኃያል ሀገር መሆኗን ገልጸው አሜሪካንና አጋሮቿን በጉልበተኝነት ከሰሱ።
ቃል አቀባዩ በመግለጫቸው፣ ኢራን በሌሎች ሀገራት ላይ ወታደራዊ ዘመቻ እንደማታካሂድ በመጥቀስ፣ ይልቁንም ምዕራባውያኑ በነጻ ሀገራት ላይ የሚፈጽሙትን ጥቃትና የመሠረተ ልማት ውድመት አጥብቀው ተችተዋል።
"ኢራን የጉልበተኞች ተቃዋሚ መሆኗን ተግባራችን ያረጋግጣል" ያሉት ባጋኢ፣ አሜሪካና እስራኤል በቀጠናው እያደረጉት ያለው ወታደራዊ እርምጃ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው ሲሉ ገልጸዋል።
የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ረድኤት እና ምልጃቸው አይለየን
🙏
ሥራው ሁሉ በዕውቀት የተመላና የተቃና ሆነ
ታላቅ ጻድቅ አባት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ትውልዳቸው ግብጽ ንሒሳ ውስጥ ነው፡፡ አባታቸው ስምዖን እናታቸው አቅሌስያ ሠላሳ ሦስት ዓመት በትዳር ሲቆዩ በሩካቤ ስጋ የተዋወቁት ለሦስት ቀናት ብቻ ነው፡፡ ይህም ልጅ እንዲሰጣቸው እግዚአብሔርን እየለመኑ ነው፡፡ አቅሌሲያ ቤተ እግዚአብሔር ገብታ ከሥላሴ ሥር ወድቃ ስትማጸን “ክብሩና ሥልጣኑ ከሰማይ ከፍታ ከፍ የሚል ንጽሕናው ከሚካኤል ከገብርኤል የሚተካከል ክህነቱ እንደ መልከጼዴቅ እንደ መጥምቁ ዮሐንስ እንደ ነቢዩ ኤልያስ የሆነ ልጅ እንቺ ተቀበይ” የሚል ድምጽ ሰማች፡፡ መጋቢት 29 ፀንሳ በታኅሣሥ 29 ደም ግባቱ እጅግ ያማረ ዓይናችን በገለጽንበት ቅጽበት ከሚታይ ነገር ላይ እንደሚያርፈው ሁሉ በተወለደበት ቅጽበት አንደበቱ ሲያመሰግን የተገኘ፣ ወንድ ልጅ ወለደች። መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል መጥቶ “የዚህ ልጅሽ ስሙ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ይሁን” አላት፡፡
ወዲያውም ሕፃኑ ከእናቱ ጭን ወርዶ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ሦስት ጊዜ ሰገዶ “ከጨለማ ወደ ብርሃን ለአወጣኸኝ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይሁን” አለ፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ባረከችው ቅዱሳን መላዕክት ዘወትር ከእርሱ ጋር ነበሩ፡፡ ከዚህም በኋላ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ሕፃኑን አባ ዘመደ ብርሃን የተባሉ አባት ላሉበት ገዳም ሰጣቸው፡፡ እሳቸውም የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ እያስተማሩ አሳድገው ሲጨርስ ዲቁና ሰጡት ፍጹም የእግዚአብሔር ጸጋ አድሮበታልና ሥራው ሁሉ በዕውቀት የተመላና የተቃና ሲሆን እንደ ቅዱስ እንጦንስም አስኬማ ሰጥተው አመንኮሱት፡፡ ከዚህም በኋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቅስናን ተቀብለው በጾም በጸሎት ተጠምደው በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመሩ፡፡
እንደ ሐዋርያትም የተአምራትና የፈውስ ሀብት ተሰጣቸውና ድውያንን የሚፈውሱ፣ ሙታንን የሚያነሡ፣ አጋንንትን የሚያወጡ ሆኑ፡፡ ወደ ሰማያት አርገው በረከትና ጸጋ የተቀበሉ፣ አጋንንትን የሚያሳድዱበት፣ ታላቅ ጸጋ ተሰጣቸው፡፡ ሰውነታቸው አንድ ክንድ ከስንዝር በሚረዝም ጠጉር የተሸፈነው አባታችን ወደ ሀገራችን መጥተው ተጋድሏቸውን ቀጠሉ፡፡
ከሰው ተለይተው ወደ ዱር ገብተው ከስድሳ አንበሶችና ከስድሳ ነብሮች ጋር የሚኖሩት አባታችን፣ እንስሳቱ እርሳቸውን የረገጡትን መሬት ልሰው ጠግበው ይኖራሉ። በሀገራች ያለውን የኃጢአት ስራ ባዩ ጊዜ በዝቋላ ሐይቅ አንድ መቶ ዓመት ተዘቅዝቀው መላው ኢትዮጵያን እንዲምርካቸው ጸልየው ቃል ኪዳን ተቀብለዋል፡፡ ገዳማውያን ይህን አብነት አድርገው ዓለምን ንቀው ለጌታችን ተገዝተዋል፤ ገዳማቱን እንርዳ በዓታችውን እናጽና፣ ከበረከታቸው እካፈል፡፡
ድጋፍ ለማድረግ፦ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444