
ያሲን ኑሩ️️ YASIN NURU
⚠️
የ"ምርጥ ሴቶች" አርአያነት፦ አስማ ቢንት አቡበከር በባሏ ቤት!
🌸
የአላህ ወዳጅና የመጀመሪያው ኸሊፋ የአቡበከር ልጅ ሆና ሳለ፤ በትዳር ሕይወቷ ውስጥ ያሳየችው ትሕትናና ጥንካሬ ለዘመኑ ሴቶች ትልቅ መመሪያ ነው። አስማ ቢንት አቡበከር (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ ትላለች፦
💍
"
ዙበይር (ኢብኑል አዋም) ባገባኝ ጊዜ፤ ከውኃ መቅጃ ግመሉና ከፈረሱ ውጭ በምድር ላይ አንዳችም ሀብት፣ አገልጋይ ወይም ንብረት አልነበረውም
።"
የቤት ውስጥ ተጋድሎዋ (አገልግሎቷ)፦
📍
የፈረሱ እረኛ ነበረች፦
"ፈረሱን እቀልብ (እመግብ) ነበር፤ ውኃም አጠጣው ነበር።"
📍
ውኃም የምትቀዳው እሷው ነበረች፦
"የውኃ ማዳበሪያውን (ባልዲውን) እጠግን ነበር፤ ውኃም እቀዳ ነበር።"
💧
📍
የማዕድ ዝግጅትም የምታዘጋጀው እሷ ነበረች፦
"ዱቄት አቦካ ነበር፤ ነገር ግን ዳቦ መጋገር አይሳካልኝም ነበር። በዚህም እውነተኛና ቅን የሆኑ የሆኑ ጎረቤቶቼ (አንሷሮች) ይጋግሩልኝ ነበር።"
🥖
✨
📍
ከባድ ሸክም መሸከም ታግዘው ነበር ፦
"ከነቢዩ ﷺ የተሰጠውንና ከቤታችን ርቆ የሚገኘውን የዙበይርን እርሻ የተምር ፍሬዎች በራሴ ላይ ተሸክሜ አመጣ ነበር።"
🌴
⛰️
💡
ወድ እህቶቼ ከዚህ ታሪክ የምንማረው ትልቅ ቁምነገር አለ፦
💎
ትዳር ማለት መደጋገፍ ነው፦
አስማ የሀብታም ልጅ ሆና ሳለ፣ ባሏ በድህነት ውስጥ እያለ ምንም ሳታማርር ከጎኑ ቆማ ደክማለች። ትዳር ማለት በደስታ ጊዜ ብቻ ሳይሆን፣ በችግር ጊዜም አብሮ መቆም ነው።
💎
እውነተኛ ክብር በትሕትና ውስጥ ነው ያለው፦
የኸሊፋ ልጅ መሆን ለባሏ እንዳትታዘዝ ወይም የቤቷን ስራ እንዳትንቅ አላደረጋትም። ትልቁ የሴት ልጅ ክብር ባሏን በማስደሰትና አላህ በሰጣት አነስተኛ ጸጋ በመርካት (ቃናዓህ) ውስጥ ነው።
💎
ሷሊህ ሴት የቤት ምሰሶ ናት፦
አስማ ለባሏ ፈረሱን እስከ መመገብና የተምር ፍሬ እስከ መሸከም ድረስ መልፋቷ፣ ለቤቷ መቃናት የከፈለችው መስዋዕትነት በታሪክ ውስጥ "ከሴቶች ሁሉ በላጯ" እንድትባል አድርጓታል።
እህቴ ሆይ! ባልሽን ማገልገልና ለቤቱ መቃናት መለፋት "ባርነት" ሳይሆን፤ የጀነት መንገድሽና የክብርሽ ዘውድ ነው። አስማን አርአያ ካደረግሽ፣ አላህ አንቺንም እንደ እርሷ በሁለቱም ዓለም ከፍ ያደርግሻል።
ያ አላህ! ለቤቶቻችን እንደ አስማ ያለ የሴትን ጽናትና እንደ ዙበይር ያለ የወንድ ጀግንነትን ስጠን።
ሶሒሕ አል-ቡኻሪ (5224)
@yasin_nuru
@yasin_nuru
የእናት ምክር
አስማ ቢንት ኻሪጃ ልጇ ስታገባ የሰጠቻት ምክሮች
ልጄ ሆይ! ከለመድሽውና ካደግሽበት ቤት ወጥተሽ
ወደ ማታውቂው ፍራሽና ወዳለመድሽው የትዳር ጓደኛ
ልትሄጂ ነው፡፡ ስለዚህ:-
◍ አንቺ መሬት ሁኚለት፤ እሱ ሰማይ ይሆንልሻል፡፡
◍ አንቺ ፍራሽ ሁኚለት፤ እሱ ምሶሶ ይሆንልሻል፡፡
◍ አንቺ ለሱ የሴት ባሪያ ሁኚለት፤ እሱ ላንቺ የወንድ
ባሪያ ይሆንልሻል፡፡
◍ አንድ ነገር ፈልገሽ ችክ አትበይ፤ ይጠላሻል፡፡
◍ ከርሱ አትራቂ፤ ይረሳሻል፡፡
◍ ወደ አንቺ ቀረብ ሲል አንቺም ወደርሱ ቅረቢ፡፡
◍ እሱ በአንቺ ከተቆጣ ንዴቱ እስኪበርድ ራቅ በይ፡፡
◍ አፍንጫውን ጠብቂለት፤ ካንቺ ጥሩ እንጂ መጥፎን እንዳያሸት
◍ መስሚያውን ጠብቂለት፤ ካንቺ ጥሩን እንጂ መጥፎን አይስማ፡፡
◍ አይኑን ጠብቂለት፤ ካንቺ ጥሩ እንጂ እንዳያይ
@yasin_nuru
@yasin_nuru
ለዘመናችን ወጣቶች የነፍስ መድኃኒት
!
~
በኢማም ኢብኑል ቀይም አልጀውዚያ ብዕር የተከተበው «አዳእ ወደዋእ»(በሽታውና መድኃኒቱ) የተሰኘው ይህ ድንቅ ኪታብ፣ በተለይም አሁን ላለንበት ዘመን ወጣቶች እጅግ አስፈላጊና አንገብጋቢ የሕይወት መመሪያ እንደሆነ አምናለሁ።ይህ ኪታብ በስሜት ማዕበል ለሚናወጠው፣ በኃጢአት አዘቅት ውስጥ ለሚዳክረው እና በፍቅር ስቃይ ለሚብሰለሰለው ልብ ሁሉ እንደ ፈዋሽ መድሐኒት ነው።
በተለያዩ ወንጀሎች ለተፈተነና ከዚህ አዙሪት መውጫ ላጣ ወጣት «አዳእ ወደዋእ»የነፍስን በሽታዎች ምንጭ በማሳየት ዘላቂ መፍትሔን ይጠቁማል።
በተለያዩ ወንጀሎች ለተፈተነ ልብ ሁሉ ይህ ኪታብ እንደ መፍተሔ ሆኖ ያገለግላል። ወንጀል በህይወታችን፣ በስኬታችንና ከአላህ ጋር ባለን ግንኙነት ላይ የሚያመጣውን ከባድ ተጽዕኖ በዝርዝር በማስረጃ አስደግፎ ያሳየናል። ወንጀልን እንደ ቀላል ነገር እንድናይ የሚያደርገንን የሸይጣን ጉትጎታ በማክሸፍ፣ የኃጢአትን አስከፊነት በልቦናችን እንዲሰርጽ ያደርጋል። ይህን በማድረጉም ከወንጀል እንድንርቅና ወደ አላህ ተውበት በማድረግ እንድንመለስ ብርቱ ጉልበት ይሰጠናል።
በተለይ በሀራም ፍቅር ግንኙነት ልባቸው ተይዞ ለሚሰቃዩ፣ ሌት ተቀን ስላፈቀሩት ሰው በማሰብ ለተንገላቱ ወጣቶች «አዳእ ወ'ደዋእ» ከኪታብም በላይ ነው። እሱ የቅርብ ወዳጅ፣ መካሪና አጽናኝ ነው። ኢብኑል ቀይም ይህንን የልብ ስብራትና ስቃይ በጥልቅ በመረዳት፣ ከዚህ አዙሪት መውጫ መንገዱን በግልጽ ያሳያሉ። ልብን ከፍጡራን ጥገኝነት ነጻ አውጥቶ፣ ፍቅርን ሁሉ ወደሚገባው አንድ አላህ ብቻ እንድናደርግ ይመክራል። ያፈቀሩትን ሰው ለመርሳት እና ልብን ከዚህ እስራት ለማላቀቅ የሚረዱ ተግባራዊና መንፈሳዊ መፍትሄዎችን በማቅረብ፣ ወደ እውነተኛ የልብ እርጋታ ይመራል።
ሐቂቃ ይህ ኪታብ በአንድ የተወሰነ የህብረተሰብ ክፍል ብቻ ተወስኖ የሚነበብ አይደለም። ይልቁንም፣ ልብ ያለውና ስለልቡ ጤንነት የሚጨነቅ እያንዳንዱ ሙስሊም ሊያነበው፣ ሊረዳውና በህይወቱ ሊተገብረው የሚገባ የህይወት መመሪያ ነው። ልክ አካላችን ሲታመም ወደ ሀኪም እንደምንፈጥነው፣ ኢማናችን ሲታመም፣ በጭንቀትና በኃጢአት ስሜት ስንወድቅም የልብ ሀኪሞችን ምክር መሻት አለብን። ኢብኑል ቀይም በዚህ ኪታባቸው ያንን ሀኪም ሆነውልናል።
ስለዚህ፣ ወንድሜ ሆይ! እህቴ ሆይ! በህይወትህ ውስጥ መፍትሄ ያጣህለት የሚመስል ችግር አለብህን? በወንጀል አዘቅት ውስጥ ሰጥመህ መውጫ መንገድ ጠፍቶብሃልን? ልብህ በማይገባው ፍቅር ታስሮ ነጻ መውጣት ከብዶሃልን? እንግዲያውስ ይህን ውድ ኪታብ አንሳና ማንበብ ጀምር። በውስጡ ለህመምህ ፈውስን፣ ለጥያቄህ መልስን፣ ለጭንቀትህም እርጋታን ታገኝበታለህ።
እኛም አንድ ቀን በ አላህ ፍቃድ ሙኽተሶሩንም ቢሆን በዚሁ በቴሌ ግራም እንደምንቀራው ተስፋ አለኝ!
አቡ ሱፍያን
@yasin_nuru
@yasin_nuru
ራሱን ባጠፋ ሰው ላይ ሶላተል ጀናዛ መስገድ
~
በኢስላም ራስን ማጥፋት ትልቅ ወንጀል ነው። ሆነ ብሎ ራሱን ያጠፋ ሰው ከባድ ወንጀል ነው የፈፀመው።
ይሄ ማለት ግን አላህ እንዲምረው ዱዓእ ማድረግ እና በሱ ላይ ሶላተል ጀናዛ መስገድ አይቻልም ማለት አይደለም።
እንዲያውም ይበልጥ ዱዓእ ያስፈልገዋል። ራስን ማጥፋት ከኢስላም አያስወጣም። ሙስሊምነቱ ከታወቀ ደግሞ በሱ ላይ ሶላተል ጀናዛ መስገድ አይከለከልም።
ነብያችን ﷺ ራሱን ባጠፋ ሰው ላይ ያልሰገዱት ከዚህ ጥፋት ሰዎችን ለማስጠንቀቅ ነው። እንጂ ሌሎች እንዳይሰግዱበት አልከለከሉም።
በተመሳሳይ ሁኔታ በማህበረሰብ ውስጥ ከፍ ያለ ቦታ ያለው በመሆኑ ሶላተል ጀናዛ አለመስገዱ ሌሎችን የሚያስደነግጥ የሆነ ሰው ባይሰግድ ተመራጭ ይሆናል።
ሌሎች ሰዎች ግን ለሟች እንደ ማንኛውም ሙስሊም ዱዓእ ሊያደርጉለት፣ ሶላተል ጀናዛ ሊሰግዱበት ይወደዳል።
ኢብኑ ሙነወር
@yasin_nuru
@yasin_nuru
ክብደትሽ ቀነሰም ጨመረም አትጨነቂ
🌙
ጨረቃ አንዳንዴ ግማሸ ናት
አንዳንድ- ግዜም ሙሉ ናት
በሁለቱም ጊዜ ጨረቃ ጨረቃ ናት
እና አንቺም ሰው ነሽ አትጨነቂ
🙌
አለ አንዱ። እንዴት ነው?
@yasin_nuru
#በቁርአን_ሥማቸውና_ታሪካቸው_የተወሱ_ነቢያቶቸ_ሥም
!
1. አደም
2. ኢድሪስ
3. ኑሕ
4. ሁድ
5. ሷሊህ
6. ኢብራሂም
7. ሎጥ
8. ኢስማዒል
9. ኢስሐቅ
10. የዕቁብ
11.ዩሱፍ
12. አዩብ
13. ሹዐይብ
14.ሃሩን
15 ሙሳ
16. አል የስዕ
17. ዙልኪፍል
18.ዳዉድ
19. ሱለይማን
20. ኢልያስ
21 ዩኑስ
22. ዘከርያ
23. ያህያ
24. ኢሳ (ኢየሱስ)
25. ሙሓመድ ናቸው (በሁሉም የአላህ ሰላምና ሰላት ይውረድ)
ከላይ ከተዘረዘሩት ሃያ አምስት መልእክተኞች አምስቱ በደረጃ ከሁሉም የበለጡ ሲሆኑ በቁርአን መከራን ቻይና ታጋሽ (ኡሉልዐዝም) በመባል ይታወቃሉ እነሱም :-
1. ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም)
2. ነብዩ ኢብራሂም (ዓለይሂ ሰላም)
3. ነብዩ ሙሳ (ዓለይሂ ሰላም)
4. ነብዩ ኢሳ (ዓለይሂ ሰላም)
5. ነብዩ ኑሕ (ዐለይሂ ሰላም) ናቸው
@yasin_nuru
@yasin_nuru
የሰዎች ሐቅ
‼
=========
(አላህ ዝም ብሎ የማያልፈው አደገኛው መዝገብ!)
||
ታላቁ ዓሊም አልመናዊ እንዲህ ይላሉ፦
قال المناوي رحمه الله:
👋🏻
"أكثر ما يُدخل الموحِّدين النَّار مظالم العباد، فديوان العباد هو الديوان الذي لا يُترك".
📚
[فيض القدير للمناوي ٣/ ٧٥٧، والتيسير بشرح الجامع الصغير ٣/ ٢٩٢]
«በአላህ አንድነት ያመኑ ሰዎችን (ሙወሒዶችን) በብዛት ወደ ጀሀነም የሚያስገባቸው የአላህን ባሮችን (ሰዎችን) መበደል ነው። ምክንያቱም የሰዎች ሐቅ (የበደል) መዝገብ በጭራሽ ዝም ተብሎ (ሳይተሳሰቡ) የማይታለፍ መዝገብ ነውና።»
ብዙዎቻችን አላህን እንፈራለን፤ እንሰግዳለን፣ እንፆማለን፣ ቁርኣን እንቀራለን። አላህ ዘንድ ያለን መልካም ሥራ (ሐሰናት) ተራራ የሚያክል ሊሆን ይችላል። ነገር ግን አንድ እጅግ የምንዘናጋበት ትልቅ አደጋ አለ... እርሱም የሰዎች ሐቅ ነው።
በእስልምና አስተምህሮ መሠረት የቂያማ ዕለት የወንጀፅ መዝገቦች (ዲዋን) በሦስት ይከፈላሉ፡-
ፈጽሞ ይቅር የማይባለው
መዝገብ፡-
በአላህ ላይ ማጋራት (ሺርክ)።
አላህ ከሻ ይቅር የሚለው መዝገብ፡-
በአንተና በአላህ መካከል ያለ
(የአላህን ሐቅ ማጓደል)።
አላህ ፈጽሞ ዝም ብሎ የማያልፈው መዝገብ፡-
በአንተና በሰዎች መካከል ያለ (የሰዎችን ሐቅ መብላት/መበደል)።
እህቴ/ወንድሜ ሆይ... አላህን ብትበድል፣ ጌታህ አዛኝና መሐሪ (አር-ረሕማን) ነውና በእዝነቱ ብቻ ይቅር ሊልህ ይችላል።
ሰውን ከበደልክ ግን፣ ፍትሐዊው አላህ ያንተን ሐሰናት (መልካም ሥራህን) ቀንሶ ለተበዳዩ በመስጠት ፍትህን ያሰፍናል እንጂ፣ ዝም ብሎ አያልፈውም። ሐሰናት ከፍሎ እዳህን ካልሞላ የርሱ ወንጀል ተቀንሶ ይጫንብሃል።
ነብዩ ሙሐመድ ﷺ «ትክክለኛው ከሳሪ (ሙፍሊስ) ማን እንደሆነ ታውቃላችሁን?» ብለው ሶሐባዎችን ሲጠይቁ፡- «የቂያማ ዕለት
በተራራ የሚያክል ሶላት፣ ፆምና ሰደቃ መጥቶ፤ ነገር ግን በዱንያ ላይ የዚህን ስም አጥፍቶ፣ የዚያን ገንዘብ በልቶ፣ ሌላኛውን ደግሞ ደብድቦና አስለቅሶ የሚመጣ ሰው ነው። አላህም ከተራራ የሚያክለው መልካም ስራው ላይ እየቀነሰ ለተበዳዮቹ ይሰጣል። መልካም
ስራው ሲያልቅበት፣ ከተበዳዮቹ ወንጀል ላይ እየተወሰደ በእርሱ ላይ ይጫንበትና ወደ ጀሀነም ይወረወራል» ብለዋል! (ሙስሊም ዘግበውታል)
እስኪ ራሳችንን እንጠይቅ፡-
በሶሻል ሚዲያ ስንቱን ሰደብን? ስንቱን አብጠለጠልን?
የስንቱን ምስኪን ገንዘብ፣ የየቲም ሐቅ አጓደልን?
በየቤታችን ሚስቶቻችንን፣ ባሎቻችንን፣ ሰራተኞቻችንን ምን ያህል አስለቀስን?
ስንቱን በሐሜት (በጚባ) ገመድነው?
ወላሂ የሰዎች ሐቅ ከባድ ነው
‼
መፍትሔው፡- የመገበያያ ገንዘብ ዲናር እና ዶላር፣ ብርና ሪያል በሌለበት፣ የሰው ልጅ በገዛ እናቱና አባቱ ላይ ሐሰናት (መልካም ሥራ) በሚሳሳበት
በዚያ በጭንቅ ቀን ከመዋረዳችን በፊት... ዛሬውኑ በዱንያ ላይ እያለን እንተሳሰብ! የበደልነውን ይቅርታ እንጠይቅ፣ የወሰድነውን ሐቅ እንመልስ። ምላሳችንን ሰውን ከመተቸትና ከማማት እንጠብቅ።
አላህ ሆይ! ሰውን ከመበደልም ሆነ በሰው ከመበደል፣ የሰውን ሐቅ አጉድሎ ባዶ እጅን አንተ ፊት ከመቆም አንተው በራሕመትህ ጠብቀን!
@yasin_nuru
@yasin_nuru
#ሩሱል_ሰለላሁ_አለይሂ_ወሰለም_እንዲህ_ብለዋል
።
“አያተል ኩርሲይ የቀራ (ያነበበ) ከሁሉም የግዴታ ሶላቶች በኋላ፤ ጀነት ለመግባት የሚከለክለው ምንም ነገር የለም ከሞት በስተቀር።”
“አላህ ባሪያውን በመርዳት ላይ ነው። ባሪያው ወንድሙን እስከረዳ ድረስ።”
“በሽተኛን ጠይቁ፣ ጀናዛን ሸኙ አኼራን ያስታውሳቹኋልና።”
“አላህ እንዲህ ብሏል፦ ‘የሰው ልጅ ዘመንን (ጊዜን) ይሳደባል። ዘመን ማለት እኔ ነኝ። ቀንም ሆነ ሌሊት በእኔ እጅ’ ናቸው።”
“በአላህ እምላለሁ! በናንተ ላይ ድህነትን አልፈራላችሁም። ነገር ግን የምፍራላችሁ ዱኒያ ከናንተ በፊት ለነበሩት ሰዎች ተዘርግታ እንደነበረችው ለናንተም ተዘርግታ ከዚያም እነርሱ እንደተፎካከሩት እናንተም ተፎካክራችሁ እነሱን እንዳጠፋቻቸው እናንተንም እንዳታጠፋችሁ ነው።”
@yasin_nuru
@yasin_nuru
አዋጅ... አዋጅ
📢
አክሱም ላይ አዋጅ ወቷል፣ ልብን የሚያደማ
ህግን አፅድቀዋል፣ሙስሊሙን አግልለው፣
በአድባራት ብቻ፣ ስብሰባውን ጠርተው፤
በትምርት ገበታ፣ ሂጃብ ላይለበስ፤
በጁምዓ ቀን ሙስሊም በጠቅላላ፣ መስጅድ ደጅ ላይደርስ፤
ባካባቢው ያሉ መስጅዶች በሙሉ፣
ጀንበሯ ሳትጠልቅ፣ እንዲዘጋ አሉ፣
አዛን እንዳይሰማ በማጉሊያ በስፒከር፣
ህግን አውጥተዋል፣ ያለምንም ድንበር፤
ሙስሊም ከሞተ፣ ለመቅበር ሲሄዱ፣
ከልክለዋቸዋል፣ ጀናዛን ላይወስዱ...
@yasin_nuru
@yasin_nuru
©
ቁርዓን የወረደበት ጠቅላላ ጊዜ፦ 23 ዓመታት።
©
በመካ የወረደው፦ ለ13 ዓመታት።
©
በመዲና የወረደው፦ ለ10 ዓመታት።
©
የክፍሎች (ጁዝ) ብዛት፦ 30 ጁዝ፡፡
©
የሂዝብ (Hizb) ብዛት፦ 60 ሂዝብ።
☺
የምዕራፎች (ሱራ) ብዛት፦ 114 ሱራዎች።
☺
የሩብ (አርባአ) ብዛት፦ 240 ሩብ።
☞ የቁርዓን ስሞች ብዛት፦ 55 ስሞች አሉት።
©
የቃላት ብዛት፦ 77,439 ቃላት።
❤
የአንቀጸች (አያት) ብዛት፦ 6,236 አንቀጸች።
©
የፊደላት ብዛት- 321,250 ፊደላት፡፡
©
ታላቋ ሱራ፦ ሱረቱ አል-ፋቲሃ።
©
ታላቋ አንቀጽ (አያህ)፦ አያተል ኩርሲ፡፡
©
ረጅሟ ሱራ፦ ሱረቱ አል-በቀራህ።
©
ረጅሟ አንቀጽ (አያህ)፦ የአዳይን (የብድር) አንቀጽ።
©
ረጅሙ ቃል፦ ''ፋ አስቀይናኩሙሁ'' (በሱረቱ አል-ሒጅር የሚገኝ)።
©
አጭሩ ቃል፦ ''ጣህ'' (ወይም ''ያሲን'')።
©
የቁርዓንን አንድ ሶስተኛ የምታከለው ሱራ፦ ሱረቱ አል-ኢኽላስ፡፡
☞ የቁርዓን ልብ የተባለቸው ሱራ፦ ሱረቱ ያሲን።
©
የቁርዓን ሙሽራ የተባለችው ሱራ፦ ሱረቱ አር-ራህማን፡፡
❤
የቁርዓን መካከለኛ ነጥብ (አጋማሽ) ላይ የሚገኘው ቃል፦
''ወልያተለጦፍ'' (በሱረቱ አል-ካህፍ የሚገኝ)።
@yasin_nuru
@yasin_nuru