Select your region
and interface language
We’ll show relevant
Telegram channels and features
Region
avatar

Al Ain Amharic አል ዐይን አማርኛ

alainamharic
አል-አይን የአማርኛ ዜና ድረ-ገፅ ሲሆን ፖለቲካዊ፡ኢኮኖሚያዊና ስፖርታዊ ዜና በዓለምአቀፍ ደረጃ በተአማኒነት የሚያቀርብ አንዱ የአል-አይን ሚዲያ ፕላት ፎርም ኔትወርክ ነው፡
Subscribers
89 600
24 hours
100
30 days
-500
Post views
72 487
ER
81,02%
Posts (30d)
Characters in post
309
Insights from AI analysis of channel posts
Channel category
Other
Audience gender
Mixed audience
Audience age
-
Audience financial status
Mixed
Audience professions
Others
Summary
-
March 19, 09:16

ቱርክ የፕሬዝደንት ኢርዶጋንን ዋና ተቀናቃኝ አሰረች
የኢስታንቡል ገዥ ቢሮ እስሩን ተከትሎ በከተማዋ ሁሉም ስብሰባዎች እና ተቃውሞዎች እንዳይካሄዱ ለአራት ቀናት የሚቆይ እግድ አስተላልፏል።
https://bit.ly/3FF7NRt

March 19, 08:24

ለ22 ዓመት ሴት መስሎ በሴቶች ገዳም ውስጥ የኖረው ሰው
የሚረዳው አጥቶ ወደ ገዳም የገባው ሰው በመጨረሻም ጾታው ሲታወቅበት ከገዳም መውጣቱ ተገልጿል
በገዳሙ ውስጥ ከሴቶች ጋር በሚኖርበት ወቅት ወንድነቱ እንዳይታወቅበት ከባድ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል
ተጨማሪ ያንብቡ
https://bit.ly/3E1XW7D

March 19, 07:50

ኤርትራ በትግራይ ክልልም ሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳዮች ጣልቃ እንደማትገባ ገለጸች
የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በሰጡት መግለጫ የኢትዮጵያን የወደብ ጥያቄ “ጊዜ ያለፈበት” ሲሉ ተችትዋል። አዲስ አበባ አስመራን ለውስጥ ችግሮቿ ተጠያቂ ከማድረግ እንድትቆጠብም አሳስበዋል።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ-
https://bit.ly/4iCgfit

March 19, 07:00
Media unavailable
4
Show in Telegram

⭕️
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ሼክ ታህኖን ቢን ዛይድን በዋይት ኃውስ ተቀብለው አነጋገሩ
📌
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአሜሪካ ጉብኝት እያደረጉ የሚገኙትን የአረብ ኢምሬትስ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪና የአቡዳቢ ምክትል አስተዳዳሪ ሼክ ታህኖን ቢን ዛይድ አል ናህያንን በዋይት ኃውስ ተቀብለው አነጋግረዋል።
📌
በዋይት ኃውስ በነበራቸው ቆይታም በሁለቱ ሀገራት ስትራቴጂካዊ አጋርነት፣ በፀጥታ፣ኢኮኖሚያዊ እና ቴክኖሎጂያዊ ትብብርን ጨምሮ በተለያዩ ዘርፎች ላይ ውይይት አድርገዋል።
📌
ፕሬዝዳንት ትራምፕ "የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እና አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ እና በአለም ላይ ሰላም እና ደህንነትን ለማስፈን በጋራ የሚሰሩ የሁልጊዜ አጋር ናቸው" ሲሉም ገልጸዋል።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ-
https://bit.ly/42dav9o

March 19, 06:22

“ከአረብ ኢምሬትስ ጋር ያለን ግንኙነት በታሪክ ጠንካራ ነው”- ትራምፕ
ፕሬዝዳንት ትራምፕ ሼክ ታህኖን ቢን ዛይድን በዋይት ኃውስ ተቀብለው አነጋረዋል። የአረብ ኢምሬትስ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪና የአቡዳቢ ም/አስተዳዳሪ ሼክ ታህኖን ቢን ዛይድ በአሜሪካ ጉብኝ እያደረጉ ነው።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ-
https://bit.ly/42dav9o

March 19, 05:15
Media unavailable
1
Show in Telegram

ፑቲን እና ትራምፕ በተጠባቂው የስልክ ውይይታቸው በምን ጉዳዮች ላይ ተነጋገሩ?
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚ ፑቲን በስልክ ውይይት ማድረጋቸውን ተነግሯል።
ሁለቱ መሪዎች 1 ሰዓት ከ30 ደቂቃ በፈጀ የስልክ ውይይታቸው የዩክሬን ጦርትና የሁለትዮሽ ግንኙነትን ማደስ የውይይታቸው አካል ነበር።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤
https://bit.ly/4kYMY3n

March 19, 03:45
Media unavailable
1
Show in Telegram

አቃቢ ህግ በእነ ዮሀንስ ቧያለው መዝገብ ስር በተከሰሱ ተጠርጣሪዎች ላይ ምስክሮችን ማሰማት ጀመረ
የፍትህ ሚኒስቴር በእነ ዮሀንስ ቧያለው መዝገብ ባሉ 52 ተጠርጣሪዎች ላይ የፖለቲካ ርዕዮትን በሀይል ለማስፈጸም ተንቀሳቅሰዋል፣ በ1996 ዓም የወጣውን የወንጀል ህግ እንዲሁም የሽብር ወንጀሎችን ለመከላከል የወጣውን ህግ ጥሰዋል በሚል ከአንድ ዓመት በፊት ክስ መመስረቱ ይታወሳል።
ከ52ቱ ተከሳሾች መካከል 16ቱ ተከሳሾች አዲስ አበባ ልደታ በሚገኘው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ህገ መንግስት እና ሽብር ወንጀሎች ችሎት የቀረቡ ሲሆን የአቃቢ ህግ ምስክሮች በተከሳሾች ላይ የምስክርነት ቃላቸውን እንደሰጡ የተከሳሾች ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአል ዐይን ተናግረዋል።
አቃቢ ህግ ተከሳሾቹ ባስተላለፉት ትዕዛዝ ምክንያት የደረሱ ጉዳቶችን ያስረዱልኛል ያላቸውን ምስክሮች አቅርቧል።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤
https://bit.ly/4iemZmZ

March 19, 01:34
Media unavailable
1
Show in Telegram

ኢራን የአሜሪካ ሰው አልባ አውሮፕላን ማባረሯን አስታወቀች
የአሜሪካ ጦር ንብረት ነው የተባለው ሰው አልባ አውሮፕላን በቴህራን አቅራቢያ ቅኝት በማድረግ ላይ ነበር ተብሏል።
የኢራኑ ኤፍ-14 የተሰኘው የውጊያ አውሮፕላን የአሜሪካ ሰው አልባ የስለላ አውሮፕላንን እንዳባረረ ተገልጿል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትሩዝ ሶሻል በተሰኘው የማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ላይ ባጋሩት ጽሁፍ " በየመን ያለው ሁቲ ቡድን ለሚያደርገው እያንዳንዱ ጥቃት ሀላፊነቱን የምትወስደው ኢራን ናት" ብለዋል።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤
https://bit.ly/4kxRVQG

March 18, 23:33
Media unavailable
1
Show in Telegram

አረብ ኢምሬትስ እስራኤል በጋዝ የፈጸመችውን የአየር ድብደባ በጽኑ አወገዘች
የአረብ ኤሚሬትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፤ ባለፈው ጥር ወር የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት በመጣስ ተጨማሪ ንጹሐን ጉዳትን በማስከተል በጋዛ ሰርጥ የሚታየውን ሰብዓዊ አደጋ የሚያባብስ ነው በማለት ማስጠንቀቁን የኤሚሬትስ የዜና አገልግሎት ዘግቧል።
ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ሁኔታውን ለማርገብ አስቸኳይ እርምጃዎችን እንዲወስድ እና አፋጣኝ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እና ሰላማዊ ዜጎችን ለመጠበቅ ሁሉንም ጥረቶችን እንዲያደርጉ ጠይቋል።
ከአረብ ኢምሬትስ በተጨማሪም ግብጽ፣ ቱርክ፣ ቻይና እና ሩሲያ ጨምሮ በርካታ ሀገራት በጋዛ የተፈጸመውን ጥቃት አውግዘዋል።
ጥቃቱን እነማን አወገዙ? በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤
https://bit.ly/3XXqN3K

March 18, 22:55

ሼክ ታህኖን ቢን ዛይድ ከአሜሪካ የግምጃ ቤት ኃላፊ ጋር ተወያዩ
ስለ ቀጣይ ጊዜ ኢንቨስምት፣ ቴክኖሎጂ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በኢነርጂና በንግድ አጋርነት ላይ መክረዋል። የአረብ ኢምሬትስ ብሄራዊ ደህንነት አማካሪና የአቡዳቢ ም/አስተዳዳሪ ሼክ ታህኖን ቢን ዛይድ በአሜሪካ ጉብኝ እያደረጉ ነው።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤
https://bit.ly/4iclcin