Select your region
and interface language
We’ll show relevant
Telegram channels and features
Region
avatar

Nejashi Printing Press

nejashipp
ይህ የነጃሺ ማተሚያ ቤት ኦፊሻል የቴሌግራም ቻናል ነው። የተለያዩ ጠቃሚ መልዕክቶችን፣ አዳዲስ የህትመት ውጤቶቻችንና አገልግሎቶቻችንን ተከታተሉን፣ ለሌላውም ሼር አድርጉ።
Subscribers
4 650
24 hours
-1
30 days
-55
Post views
2 283
ER
49,1%
Posts (30d)
12
Characters in post
693
Insights from AI analysis of channel posts
Channel category
Books
Audience gender
Female
Audience age
35-44
Audience financial status
Middle
Audience professions
Education
Summary
August 22, 15:51

ከነቢዩ ሰ.ዐ.ወ ባህርያት
***
41. ለሴትም ሆነ ለወንድ፤ በዕድሜ ለገፉ ሰዎች፣ ህፃን ልጅም ይሁን ጎልማሳ ላናገራቸው ሁሉ ይቆማሉ፡፡ ያማከራቸውን ያማክራሉ፡፡
42. ተናጋሪ ንግግሩን ሳይጨርስ አይናገሩም፡፡ እጃቸውን የያዛቸው ሰው እስካልለቀቃቸው ድረስ ቀድመው አይለቁም፡፡
43. አንድ ሰው ከርሳቸው አንዳች ነገር የፈለገ እንደሆነ ሳይሰጡት አይመልሱትም፤ የሌላቸው ቢሆን እኳ ከሰሓቦቻቸው ይጠይቁለታል፡፡
44. በሐቅ ጉዳይ ላይ ማንኛውም ሰው፤ ደካማም ይሁን ጠንካራ፤ ድሃም ሆነ ሀብታም እርሳቸው ዘንድ እኩል ነው፡፡
45. አቀማመጣቸው የትዕግስት እና የታማኝነት አቀማመጥ ነው፡፡
46. እርሳቸው ዘንድ ይበልጥ ደረጃ ያለው ሰው፤ ይበልጥ አላህን የሚፈራ ነው ።
47. ባህሪያቸው ለሁሉም የሚመች ገር ነው።
48. አቀራረባቸው ለረጅም ጊዜ እንደሚተዋወቅ ሰው ነው፡፡
49. ማህበራዊ ኑሮአቸው ልስላሴና መግባባት የተሞላበት ነው፡፡
50. ተራግመው አያውቁም፣ አያማርሩም፣ አይጮሁም፣ የሚያነውሩና የሚያጥላሉ አይደሉም፡፡
51. ሰዎችን ባጠፉ ጊዜ መምከርና ማስተማር የፈለጉ እንደሆነ በቀጥታ ስማቸውን በመጥራት ሳይሆን ጥፋቱን በማንሳት ‹ምን ዓይነት ሰዎች ናቸው እንዲህ እንዲህ የሚያደርጉት› ይሉ ነበር፡፡
52. ቀልድ አያበዙም፡፡ ይቀልዳሉ፣ ነገርግን ሐቅን እንጂ አይናገሩም፡፡
53.ከማይፈልጉት ነገር ችላ ያሉ ናቸው፡፡ አያስቡትም፣ አይከተሉትም።
54. አላህ የመረጠላቸውን ነገር ይመርጣሉ፡፡ በመረጠላቸው ነገርም ይረካሉ ።
55. አንድንም ሰው ዘልፈውም ሆነ በድለው አያውቁም፡፡ የጎዳሁት ሰው ካለ ዛሬውኑ ካሳውን ይቀበለኝ ይሉ ነበር፡፡
56. የሰዎችን ገመና አይከታተሉም፡፡ ሰዎች ከሰዎች ይልቅ ወደራሳቸው ችግር እንዲመለከቱ ይመክሩ ነበር፡፡
57.ሲናገሩ በዙሪያቸው ያሉ ሰዎች በራሳቸው ላይ ወፎች የተቀመጡ በሚመስል መልኩ በጥሞና ያዳምጧቸዋል፡፡
58. ባልደረቦቻቸው እርሳቸው ዝም ሲሉ ብቻ ጠብቀው ይናገራሉ፡፡
59. ሰሓቦቻቸው በሚስቁት ይስቃሉ፡፡ እነርሱ በሚደነቁት ነገር ይደነቃሉ፡፡
60.*ንግግር ለማይችል አላዋቂንም ባላገር/ዘላን ሰውን ይታገሳሉ፡፡
61.ከአንድም ሰው ሙገሳን የሚፈልጉ አይደሉም፡፡ የሚኖሩትም ሆነ የሚሰሩት ለአላህ (ሱ.ወ.) ነው፡፡
62. ሰዎችየዒልም (ዕውቀት) ባለቤቶች ዘንድ እንዲያርፉ፣ ከዕውቀት ማዕድም እንዲቋደሱ ይመክራሉ፡፡
63.አንድ ሰው ቢቆጥር የተናገሩትን ቃላት መቁጠር በሚችል መልኩ ነው የሚያወሩት፡፡ ንግግር አያበዙም፡፡
64. ሲናገሩ የሚሰማቸው ሁሉ ለረዳቸው በሚችል መልኩ ይናገራሉ፡፡
65. ለንግግር ማሳመርም ሆነ ለመምሰልና ለማስመሰል አይጨናነቁም፤ አይፈላሰፉም፡፡
66. አድማጭ ይረዳቸው ዘንድ ንግግራቸውን ሶስቴ ይደጋግማሉ፡፡
67.ረጋ ባለና ግልጽ በሆነ መልኩ ይናገራሉ፡፡
68.ሲናገሩም ሆነ ቁርኣን ሲያነቡ ድምፃቸው ውብ ነው፡፡
69. ከልጆች ጋር ይቀልዳሉ፡፡ ህፃናትን ያጫውታሉ፡፡ 70. ሕፃናት ልጆችን ተሸክመው ይሰግዳሉ፡፡
70. ለባልደረቦቻቸው ስኬትንና በረከትን ይለምናሉ፡፡
71. ቁርኣን ሲነበብ ከሌላ ሰው መስማት ይወዳሉ፡፡
72. በግመላቸው ላይ ሆነውም ጭምር ቁርኣን ያነቡ ነበር፡፡
73. አካሄዳቸው ያማረና ፈጠን ያለ ነው፡፡ ሲራመዱ ምድር የምትጠቀለልላቸው ይመስላሉ፡፡
74. ሲፀዳዱ ስውር ስትር ብለው ከሰዎች ዓይን ርቀው ነው፡፡
75.,መዓዛቸው እጅግ ያውዳል፡፡ ላባቸው እንደሚስክ ይሸታል፡፡
76. እጅግ መልካም ሰው፣ እጅግ ለጋሽና እጅግ ጀግና ናቸው፡፡
77. እጅግ በሳልና አዋቂ፤ አቻ የሌላቸው ብልሃተኛም ናቸው፡፡
78. ሲመፀውቱ ድህነትን የማይፈራ ዓይነት ሰው መመጽወትን ይመፀውታሉ፡፡
79. ለሻጭ መብት ይሠጣሉ። በመሸጥና ባለመሸጥ መካከል አማራጭ ያቀርቡለታል፡፡
80. ከአንዱ ወንድማቸው ሊበድሩ ይችላል፡፡ ንብረታቸው በዕዳ የሚያዝበት ሁኔታ ይኖራል።
https://t.me/Nejashipp

August 18, 16:04

ከነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ.) ባህርያት
****
1. የሥራና የአምልኮ ሰው ናቸው፤ ሌትም ሆነ ቀን ዕረፍት የላቸውም፡፡
2. እጅግ ቸርና እጅግ ለጋስ ናቸው፡፡
3. ታጋሽና ቁጥብ፣ ጨዋና ራሳቸውን የገዙ ናቸው፡፡
4. ያገኙትን ሰው በሰላምታ ይቀድማሉ፡፡
5. ያለ ጉዳይ ወይም ያለምክንያት አይናገሩም፡፡
6. ሲናገሩ በዝርዝር ሳይሆን ጠቅላይ በሆኑ ቃላቶች ነው፡፡
7. የአላህን ፍጥረታት በመመልከት ድንቅ ተዓምራቱን ዘወትር ያስተነትናሉ፡፡
8.ለዓለማት ህዝብ ሁሉ መስተካከል ያስባሉ ይጨነቃሉ፡፡
9. ከኩራት፣ ከመመፃደቅና ከጉራ የራቁ ናቸው፡፡
10. ዝምታ ያበዛሉ፡፡ ሀሳብ ትካዜያቸው ተከታታይ ነው፡፡
11. ገፍታራና ኮስታራ አይደሉም፡፡ በሻሻ ናቸው፡፡
12. ላያቸው ሁሉ የሚስብ ግርማ ሞገስ አላቸው፡፡
13. ትንሿን የአላህ (ሱ.ወ.) ፀጋ እንደ ትልቅ ያያሉ፡፡
14. ከበሉም ሆነ ከጠጡ በኋላ ሁሌም ያመሰግናሉ፡፡
15. አላህ (ሱ.ወ.) ከሰጣቸው ነገር አንድንም ነገር አያጣጥሉም፡፡ አይንቁም፡፡
16. ለራሳቸው ስሜት ብለው አይቆጡም፤ ለራሳቸው አይሞግቱም፡፡
17. ሁለመናቸውን ለአላህ ያሳደሩ ባርያው ናቸው፡፡
18.ለሐቅ ሲሉ ይቆጣሉ፡፡ ሐቅን እስኪያነግሱ ድረስም ዕረፍት የላቸውም፡፡
19. የተቆጡ እንደሆነ ከቦታው ዘወር ይላሉ፡፡
20. ሲደሰቱ ዐይናቸውን ዝቅ ያደርጋሉ፡፡ ድል ሲያገኙ አምላካቸውን ማመስገን ያበዛሉ፡፡
21. ሳቃቸው አብዛኛውን ጊዜ ፈገግታ ነው፡፡
22. ወደቤታቸው ሲገቡ ጊዜያቸውን ለሶስት ይከፍላሉ፡፡ ለአላህ፣ ለቤተሰባቸውና ለራሳቸው፡፡
23. ሰዎች እንዲዋድዱ ይመክራሉ፤ የተጣላን ያስታርቃሉ፤ ግንኙነታቸው ተመልሶ እንዲጠናከር ያደርጋሉ፡፡
24. የማህበረሰቡ ክብር የሚሰጠውን ሰው ያከብራሉ፡፡ በህዝቦቹ ላይም ሀላፊነት ይሰጡታል፡፡
25. ስለ ሰሓቦቻቸው ሁኔታ ይቃኛሉ፡፡ የቸገረውንና የጠፋውን ይጠይቃሉ፡፡
26. መልካምን ነገር መልካም፤ መጥፎን ነገር መጥፎ ይላሉ፡፡
27. በነገራቸው ሁሉ መካከለኛና ሚዛናዊ ናቸው፡፡
28. በዲን ጉዳይ ላይ ጽንፈኝነትም ሆነ ቸልተኝነት የለባቸውም፡፡
29. ሲታጠቡ፣ ሲለብሱ፣ ሲጫሙ፣ ፀጉራቸውን ሲያበጥሩ እንዲሁም ሌሎች መልካም ነገሮችን ሲሰሩ ቀኛቸውን ያስቀድማሉ፡፡
30. ሰሐቦቻቸው እንዳይዘናጉ ብለው በየጊዜው ይመክሯቸዋል፣ ይገስጿቸዋል፡፡
31. ሁሉንም ነገር እአላህ እንደፈቀደው ይቀበላሉ፡፡ አላህ (ሱ.ወ.) የሻላቸውን ይወዳሉ፡፡ እሱ የመረጠላቸውንም ሳይቆረቁራቸው ይቀበላሉ፡፡
32. የሕዝበ ሙስሊሙ መሪ ቢሆኑም ለየት ያለ ዙፋንም ሆነ መቀመጫ የላቸውም፡፡ አጃቢ ባንድም ሆነ ጠባቂ ሰራዊት አልነበራቸውም፡፡
33.ደሳሳ ጎጆዎች ውስጥ ነው የኖሩት፤ የቤቶቻቸው ጣሪያም ቅርብ ነው፡፡
34. አብዛኛው ምግባቸው ተምርና ውሃ ነው፡፡
35. በማኀበራዊም ሆነ የትግል ጉዳዮች ላይ የነቃ ተሳትፎ አላቸው። በከዕባ ዕድሳት ወቅት፣ የመዲና መስጂድ ሲገነባ፣ በኸንደቅ ምሽግ ቁፋሮ ጊዜ ትልቅ እገዛ አድርገው ነበር፡፡
36. ይበልጥ ወዳጆቻቸው የነበሩት በአምልኮ ተግባራት በላጮች የሆኑት ናቸው፡፡
37. እርሳቸው ዘንድ ምርጡ ሰው ለሰው ጠቃሚ የሆነ፣ ለሌሎች የሚያስብና ሌሎችን የሚያግዝ ነው፡፡
38. አላህን (ሱ.ወ.) ያወሱ ቢሆን እንጂ አይቆሙም፤ አይቀመጡም፡፡ አይተኙም፣ አይነሱም፡፡
39.ሰዎች ስብስብ ዘንድ በመጡ ጊዜ በበቃቸው ቦታ ላይ ነው የሚቀመጡት፡፡ ሰሓቦቻቸውንም በዚሁ ሥርዓት ያዙ ነበር፡፡
40. የተቀመማጧቸውን ያለ ልዩነት ያናግራሉ፡፡ እያንዳንዱ ሰው እኔን ነው የሚወዱት ብሎ እስኪያስብ ድረስ አንዱን ከሌላኛው ላይ ሳይለዩ ያቀርባሉ፡፡
500 የነቢዩ ሰ.ዐ.ወ ባህርያት መጽሐፍ
ነጃሺ ማተሚያ ቤት
ትርጉም ፦ ሙሐመድ ሰዒድ (ABX)
https://t.me/Nejashipp

August 18, 16:04
Media unavailable
1
Show in Telegram

August 17, 08:28
Media unavailable
4
Show in Telegram

August 17, 08:28
Media unavailable
1
Show in Telegram

የባዶነት ስሜት
መንስኤው እና ፈውሱ
በኡስታዛ ያስሚን ሙጃሂድ
ወደ ገበያ ተመልሷል
ነጃሺ መፃሕፍት መደብር ያገኙታል ።
ነጃሺ የዕውቀት ማዕድ

August 11, 18:03
Media unavailable
2
Show in Telegram

August 11, 12:24
Media unavailable
1
Show in Telegram

በምርጥ ሙስሊም ምሁራን ስለ ኢስላም ከተፃፉ ቆየት ካሉና የቅርብ ምርጥ መፃሕፍት መካከል እነኚህን እንጋብዛችሁ፡፡
የቱን አንብባችኋል!
1- ኢስላምን ለመረዳት ፡ ዶ/ር ዩሱፍ አል-ቀረዷዊ - አላህ ይዘንላቸው፣
2- ኢስላማዊ እሴቶች ፡ በኡስታዝ ሐሰን አዩብ
3- ኢስላም የማኅበራዊ ችግሮች መፍትሄ ፡ በኡስታዝ አቡል አዕላ አል-መውዱዲ
4- የኢስላም ድል አድራጊነት ፡ ዶ/ር ዩሱፍ አል-ቀረዷዊ
5- የኢስላማዊው ሥልጣኔ አንፀባራቂ ገጽታዎች ፡ ዶ/ር ሙስጠፋ ሲባዒ
6- የኢስላም ሁለንተናዊነት ፡ በዶ/ር ዐብደላህ አል-ቀሕጣን (ክፍል አንድ እና ሁለት)
7- ይህ ነው ኢስላም፡ ሸይኸ ዐሊ ጠንጣዊ
8- የኢስላም ጥሪ ፡ በወሒዱ ዲን ኻን
9- ኢስላም የዘመናዊ ሥልጣኔ ፈጣሪ ፡ በወሒዱ ዲን ኻን
10- የኢስላማዊ ጥበብ ውርሣችን ፡ በወሒዱ ዲን ኻን
https://t.me/Nejashipp

August 05, 09:55

https://vt.tiktok.com/ZS4ug6hNE/

July 31, 12:11
Media unavailable
1
Show in Telegram

ነጃሺ መፃሕፍት
በኤግዚቢሽን ማዕከል
ከልዩ ቅናሽ ጋር

July 28, 05:52

https://www.facebook.com/share/p/1CdY6wjokS/