
Nejashi Printing Press
https://nejashibooks.com/
https://t.me/Nejashipp
https://vt.tiktok.com/ZSCYng16B/
በዚያ ዕለትም ‘ሠንየተል ወዳዕ’ በተባለው ሥፍራ በርካታ የመዲና ሕዝብ ተሰብስቦ ምስጋናና ውዳሴ እያሰማ ተቀበላቸው፡፡ መዲና በታሪኳ እንደዚያ ቀን የደስታ እልልታ ገጥሟት አያውቅም፡፡
ዕለቱ በእርግጥም ኢስላም ጠባብ ከሆነው የመካ አስጨናቂ ሕይወት ወደ ሠፊውና አስደሳች ወደ ሆነው የመዲና ሕይወት ሽግግር ያደረገበት ታሪካዊ ቀን ነበር፡፡ የመዲና ሕዝቦች የአላህን ታላቅ በረከትና ጸጋ በደስታ ተቀብለው ምስጋናና ውዳሴ ያሰሙበት ድንቅ ዕለት፡፡ ለምን አመስጋኝ አይሆኑ!! ምድራቸው ታሪካዊውን የኢስላም ብርሃን ለዓለም እንድታደርስ ተመርጣለች፡፡ የመጨረሻውንና የነብያት ሁሉ መደምደሚያ የሆኑትን ሙሐመድን (ሰ.ዐ.ወ) ተቀብላ ለማስተናገድ ከመታደል የበለጠ ምን ልቅና ትሻለች! ዕድለኛ ከተማ፡፡ በጊዜው ሁሉም “የአላህ መልዕክተኛ! የአላህ መልዕክተኛ! ሙሐመድ!” እያለ ደስታውን ሲገልጽ ይታይ ነበር።
ዝነኛው የጠለዐል በድሩ ዐለይና ነሺዳም በዚያ ቀን ተነሸደ።
የአላህ መልዕክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) በታሪክ ገጾች የሚስተካከለው በሌለ የደመቀ አቀባበል መዲና ከገቡ በኋላ የሚያርፉበትን ሥፍራ ራሳቸው መወሰን አልፈለጉም ነበር፡፡ ከዚያ ይልቅ “ግመላቸው መለኮታዊ ምሪት” እንዳላትና እርሷ የምታርፍበትን ቦታ ትክክለኛው ማረፊያቸው እንደሆነ በማሳወቅ ጉዟቸውን ቀጠሉ፡፡ በመጨረሻም የአቡ አዩብ አል-አንሷሪ (ረ.ዐ) ቤት ሲደርሱ አቡ አዩብ (ረ.ዐ) ተሸቀዳድመው ጓዛቸውን በመያዝ እቤታቸው አስገቡት፡፡
ከ" ለዓለማት እዝነት" መጽሐፍ
ትርጉም : አቡ ቢላል
https://t.me/Nejashipp
https://www.tiktok.com/@nejashibooks
https://nejashibooks.com/
ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን ነጃሺ ማተሚያ ቤት ከዚህ በታች በተዘረዘረው ክፍት የስራ መደብ ዝርዝር መሰረት አመልካቾችን አወዳድሮ መቅጠር ይፈልጋል።
*የስራ መደቡ መጠሪያ:- የማርኬቲንግ ባለሙያ
*ብዛት:-1
*የት/ት ደረጃ:- በማርኬቲንግ ወይንም ተዛማጅ የት/ት ዘርፍ የተመረቀች/ቀ
*የስራ ልምድ:-2 አመትና ከዚያ በላይ
*ፆታ:-ሴ/ወ
*ደሞዝ:-በስምምነት
አመልካቾች የትምህርት ማስረጃችሁንና የስራ ልምዳችሁን 09_45_85_85_85 በቴሌግራም ወይንም
nejashipress@gmail.com ላይ መላክ ትችላላችሁ
ነጃሺ ማተሚያ ቤት
https://t.me/MuhammedSeidAbx
ያ ጉድጓድ ውስጥ የተጣለው፣
በባልዲ ተንጠልጥሎ ከጉድጓዱ የወጣው እና
በርካሽ ዋጋ የተሸጠው፤
ኋላ ላይም ሚኒስቴር ሆኖ፣
ቀጥሎም የግብፅ ዋና ገዥ ሊሆን ጥቂት ቀርቶት የነበረው ነቢዩ ዩሱፍ (ዐ.ሰ.) ታሪኩ ምን ያስተምረናል መሰለህ…
በዘመንህ ውስጥ የሚያጋጥሙህ ከባባድ የሕይወት ገፆች ሁሉ፣
በሕይወት ውስጥ ወደፊት የሚመጣውን እጅግ ውቡን ሕይወትህን መንገድ ለመጥረግ የተላኩ መቅድሞች ሊሆኑ ይችላሉና ታገስ!
በአላህ ላይ መልካምን ብቻ ጠርጥር!፡፡
በአያመ ተሽሪቅ ውስጥ የሚፈፀሙ ሥርዓቶች
*
ከዒድ ቀን በኋላ ያሉ ሦስቱ የዚል-ሒጃ 11ኛ፣ 12ኛ እና 13ኛ ቀናት ቀናት “አያመ ተሸሪቅ” በመባል ይታወቃሉ፡፡ የዒድ ቀናቶች ናቸው፡፡ በነኚህ ቀናት ውስጥ ይበላል፣ ይጠጣል፣ የጠጠር ውርወራ ሥርዓት ይከናወናል፡፡
ውርወራው ሰባት ሰባት ጠጠሮች በሦስት ቦታዎች ላይ በመወርወር ይከናወናል።
ቦታዎቹና ቅደም ተከተላቸውም "ጀምረቱል-ኡላ" (የመጀመሪያው ጠጠር መወርወሪያ) "ጀምረቱል ውስጧ" (የመሃለኛው) ጠጠር መወርወሪያ እና "ጀምረቱል ዐቀበህ" የመጨረሻው የጠጠር መወርወሪያ ቦታዎች ናቸው።
የመወርወሪያ ጊዜም ፀሐይ ከእኩለ-ሰማይ ወደ ምእራብ ከወረደች በኋላ ጀምሮ እስከምትጠልቅ ድረስ ባለው ወቅት ነው።
በ "ጀምረቱል ኡላ እና በ ጀምረቱል ውስጧ የጠጠር መወርወሪያ ሥፍራ ላይ ጠጠሮችን ወርውሮረው እንደጨረሱ ወደ ቂባላ ዙሮ ዱዓእ ማድረግ ይመረጣል።
በ "ጀምረቱል_ዐቀበህ" (በመጨረሻው) የጠጠር መወርወሪያ ስፍራ ላይ ግን ጠጠሮችን ወርዉሮ መመለስ እንጂ ዱዓእ አይደረግም።
ትንሹን፣ መካከለኛውንና ትልቁን (የመጨረሻውን) የጠጠር ውርወራ ሥርዓት መፈፀም ተገቢ ነው፡፡ ለእያንዳንዳቸው ሰባት ሰባት ጠጠሮች ይወረወራል፡፡
እያንዳንዱን ጠጠር ሲወረወር ተክቢራ በማድረግ ይወደዳል፡፡ ሰባቱንም ጠጠሮች አከታትሎ መወርወር ሱንና ነው፡፡
የውርወራውን ሥርዓት በቅደም ተከተል መፈፀሙ መስፈርት ነው፡፡ በትንሹ ይጀምራል፡፡ መካከለኛውን ያስከትላል፡፡ በትልቁ ያጠናቅቃል፡፡
ጠጠሮች በሚወረውሩበት ገንዳ እና በሰውዬው መካከል ሦስት ክንድ እና ከዚያ በላይ ርቀት መኖሩ ሱንና ነው፡፡ ርቀቱ ከዚያ ያነሰ ከሆነ መጣል እንጅ መወርወር አይባልምና፡፡
የጠጠር ውርወራ ሥርዓት የሚጀመርበትን ወቅት በሚመለከት ታላቁ የውርወራ ሥርዓት ከዒድ ሌሊት አጋማሽ በኋላ የሚጀመር ሲሆን ሦስቱም ከዒድ ቀን አጋማሽ በኋላ ይጀመራሉ፡፡ በአያመ ተሸሪቅ የመጀመሪያው ቀን ተጀምረው በመጨረሻው (ዒድ በዋለ በአራተኛው ቀን) ፀሐይ ከመጥለቋ በፊት ይጠናቀቃሉ፡፡
ሐጅ አድራጊ ጠጠር መወርወር ሲጀምር ‹ለበይክ…› ማለቱን ማቆም ይኖርበታል፡
ከሐጅና ዑምራ መጽሐፍ
https://t.me/Nejashipp
https://www.tiktok.com/@nejashibooks
https://nejashibooks.com/