
وذكر አስታውስ
"ጌታቹን እስክትገናኙ ድረስ ታገሱ በናንተ ላይ ዘመን አይመጣም ከሱ ቡሃላ ያለው የባሰ መጥፎ ቢሆን እንጂ"
ቡኻሪይ ዘግበውታል
ከነገራት ሁሉ ታላላቆቹ ሶስት ናቸው
1. ያለችን ትንሽ ብትሆንም ከሷ ላይ መለገስ
2. ብቻችን በተገለልን ወቅት አላህን መፍራት
3. የሚከጀል ና ሚፈራ አካል ዘንድ ሃቅን መናገር
"ተውበት ማለት /ወንጀል ላይ/ መዘውተርን መተው ነው " ማለት ነው ይላሉ ሃፊዝ ኢብኑ ረጀብ
አላህ ሙተቆችን ፈሪሀ አላሆችን በቁርአኑ ሲገልፅ መጥፎ ነገር ሰርተው ነፍሶቻቸውን በበደሉ ጊዜ አላህን አስታውሰው መሀርታውን ሚጠይቁና በስራቸው ላይ ያልዘወተሩ ናቸው የሰው ልጅ ወንጀል ከመስራት ሊድን አይችልም ዛሬ ተውበት አርጎ ነገም ሊወነጅል ይችላል ፈሪሀ አላሆችን ከሌላው የሰው ልጅ ሚለያቸው ግን ወንጀልን ሲሰሩ ውስጣቸው ይረበሻል ምድር ከመስፋቷጋ ትጠባቸዋለች ወዲያውም የተናነሱ ሆነው ማያልቅ ወደሆነው ወደ ጌታቸው መሀርታ ክጃሎት ይመለሳሉ ጌታቸውም አያሳፍራቸውም ወንጀላቸውን መማር ብቻ ሳይሆን ያንኑ ወንጀል አላህ ወደ መልካም ስራ ቀይሮ ይፅፍላቸዋል
አቡ ዘር እንዳስተላለፉ "የቂያማ ቀን አንድን ሰው ወደ አላህ ይመጣል ጌታውም የባሪያዬን ትናንሽ ወንጀሎች አቅርቡለት ይላል ይህን ይህን ፈፅመሃል ይባላል እሱም ማስተባበል አይቻለውም ትላልቅ ወንጀሎቹን እያሰበ ይጨነቃል በሁሉም ወንጀሎችህ ቦታ መልካም ስራ ተቀይሮልሃል ሲባል ግን ጌታዬ እዚህ ማላያቸው የተለያዩ ወንጀሎችን ሰርቻለው ይላል ከዛም የአላህ መልክተኛ ድዶቻቸው እስኪታዩ ሳቁ"
ሙስሊም ዘግበውታል
ኢማም ዐሊይ ዐለይሂ ሰላም እንዲህ አሉ "ከናንተ በላጩ /በወንጀል/ ተፈትኖ ተውበት ያረገው ነው ወደ ወንጀሉ ከተመለሰስ ተባሉ አላህን መሀርታ ይጠይቃል ወደሱም ይመለሳል አሉ እስከሚሞት አሉዋቸው ከሳሪው አዛኙ ሸይጣን እስኪሆን ድረስ አሉ"
ሸይጣን በሰዎች ላይ ሚገባባቸው ዋነኛዎቹ በሮች ሶስት ናቸው ይላሉ
1. ዝንጉነት
2. ስሜት
3. ቁጣ
"በምቾትም በችግርም ወቅት በሚወደውም በማይወደውም ነገር ላይ በዒባዳ ላይ የፀና ፍራቻና ሀዘን ከሌለባቸው ባሪያዎች ውስጥ ይሆናል"
ሙኽተሰር ፊቂሀል ኢስላሚይ
"ስለ ተቅዋ አላህን መፍራት ሚመክሩ ብዙ ናቸው ሚተገብሩ ግን ጥቂት ናቸው"
አሚሩል ሙዕሚኒን ዑመር ኢብኑ አብዱልዐዚዝ
"አንተ ዘንድ ወንጀልህ ቀሎ በታየህ ቁጥር አላህ ፊት ይገዝፋል አንተ ዘንድ በገዘፈ ቁጥር አላህ ፊት ይቀላል"
ፉደይል ኢብኑ ዒያድ
"ኸይር ነገራት 3 ናቸው በአላህ ማመን ዲንን መማርና ሷሊህ የሆነች ሚስት"
ኢማም ዐሊይ ኢብኑ አቢ ጣሊብ ዐለይሂሰላም
ከባዱና ትልቅ ኢማን ሚጠይቀው ነገር በአስቸጋሪ ወቅቶች ወደ አላህ ከመሸሽ በላይ በምቾት ገዜያት ወደ አላህ መሸሽ ነው